Saturday, 18 April 2015

የደቡብ አፍሪካው የስደተኛ ጠልነት መነሻው ምንድነው? // አብይ1702 //

የደቡብ አፍሪካው የስደተኛ ጠልነት መነሻው ምንድነው? 

(የሰባት ኪሎ ወቅታዊ አጭር ትንተና)
ደቡብ አፍሪካን በቅርቡ የማይከታተሉ ሰዎችን በእጅጉ ያስደነገጠ ቢኾንም በአገሪቱ ስደተኞች ላይ ያነጣጠረ ኹከት ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመርያው አይደለም። እ.ኤ.አ በግንቦት ወር 2008 አሌክሳንደር በተባለ የጆሃንስበርግ ታውንሺፕ የተነሳ ኹከት ወደ ደርባን እና ሌሎች ከተሞች ተዛምቶ ቢያንስ ለዐርባ ስደተኞች መሞት ምክንያት ኾኗል። በኹከቱ ብዙ ንብረት ወድሟል። ከዚያ በፊት እና በኋላም ቢኾን ሌሎች በርካታ አነስተኛ ጥፋቶች ተፈጽመዋል። ይህ ለብዙዎች እንቆቅልሽ ነው “በጉርብትና የሚኖሩ ሰላማዊ ስደተኞችን በእንደዚህ ዐይነት ጭካኔ ማቃጠል፣ መግደል እና መደብደብ ለምን?” የሚለው ጥያቄ ተደጋግሞ ይነሳል። በደቡብ አፍሪካ እንዲህ ዐይነት ከፍተኛ የኾነ ስደተኛ ጠልነት ለምን ተስፋፋ የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ምናልባትም ወደ አገሪቱ የመጀመርያዎቹ የዴሞክራሲ ዓመታት መለስ ብሎ መመልከት አስፈላጊ ነው።
ከኻያ ዓመታት በፊት አፓርታይድ ተገርስሶ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት ሲጀመር በደቡብ አፍሪካ ሁለት ነገሮች ተፈጠሩ። በመጀመርያ ብዙኃኑ ጥቁሮች ከጥቂት ነጮች ጭቆና ተላቀው እነርሱ በመረጡት መንግሥት አስተዳደር አማካኝነት ከነበሩበት የኢኮኖሚ ችግር እንደሚወጡ ተስፋ ሰነቁ። በጊዜው የወጡ የሕዝብ አስተያየት ጥናቶች እንደሚያሳዩት በርካቶች ከነጭ ሀብታሞች ተቀንሶ ለድኾች የሚሠጥበት የኢኮኖሚ መልሶ ማከፋፈል (economic redistribution) ይኖራል የሚል ተስፋ ነበራቸው። ከፍ ያለ የትምህርት ዕድል፣ ቀስ በቀስ የሚያድግ ገቢ፣ የተሻለ የመኖርያ ቤት የማግኘት ፍላጎት ጨመረ። በሌላ በኩል በተለይ በምዕራብ አገሮች መንግሥታት እና ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ አዲሱ ዴሞክራሲ የንብረት መብትን ይሸረሽራል፣ የኤኤንሲ መንግሥት ከመራጮች በሚመጣ ጫናም ይኹን በውስጥ ፖለቲካው ምክንያት መልሶ ለማከፋፈል ሲል ንብረት ይወርሳል፣ ከባድ ግብር ይጥላል ወዘተ . . . የሚል ስጋት ነበር።
ይኹንና የድኻ ጥቁሮች ተስፋም ይኹን የሌሎቹ ስጋት እውን አልኾነም። ማርቲን ፕላውት እና ፖል ሆልደን “Who rules South Africa?” በሚል መጽሐፋቸው እንደሚያትቱት ኤኤንሲ ሥልጣን ላይ እንደወጣ ከወሰዳቸው የመጀመርያ ‘ርምጃዎች መካከል አንዱ እ.ኤ.አ በ1955 የነጻነት ቻርተር ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ይዞት የቆየውን ሶሻሊስታዊ ኢኮኖሚ አስተሳሰብ ትቶ በቅይጥ ኢኮኖሚ መተካቱ ነበር። የቅይጥ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎቹም ቢኾኑ ብዙም ተግባራዊ ሳይደረጉ ተራግፈዋል። ግራ ዘመም የሚባለው እና በኔልሰን ማንዴላ ይደገፍ የነበረው መልሶ የመገንባት እና የልማት ፕሮግራም (Reconstruction and Development Programme) ለሁለት ዓመታት እንኳን በቅጡ ተግባራዊ ሳይኾን በጊዜው ምክትል ፕሬዝዳንት በነበሩት እና አሁን በተለያዩ የአፍሪካ አገራት እየተዘዋወሩ ‘ኒዮ-ሊበራሊዝምን እቃወማለሁ’ እያሉ በሚናገሩት ታቦ ምቤኪ ውትወታ ወደ ቀኝ ባዘመመው የዕድገት፣ የሥራ እና የመልሶ ማከፋፈል ስትራቴጂ (Growth, Employment and Redistribution Strategy) ተተካ። በመጀመርያው ፕሮግራም ተጀምረው የነበሩ የመኖርያ ቤት አቅርቦት ፕሮጀክቶች፣ ለድኾች የሚሰጡ የተለያዩ ድጎማዎች፣ የመጠጥ ውሃ፣ ንጹሕ የመጻዳጃ ቤቶች እና መብራት ማስፋፋት በሁለተኛው ፕሮግራም እየተዳከሙ መጡ። እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ ለድኻ ደጋፊ ፖሊሲዎች ብዙ ቁብ ያልነበረው የዓለም ባንክ ሳይቀር ይህ የፖሊሲ ለውጥ አስጨንቆት የደቡብ አፍሪካ መንግሥት መጠነኛ ማሻሻያ እንዲያደርግ ምክር ለግሶ ነበር። ኤኤንሲ ሥልጣን ላይ ከወጣ ከዐሥር ዓመታት በኋላ በአገሪቱ የተመዘገበው ኢ-እኩልነት እ.ኤ.አ በ1970ዎቹ እና በ1980ዎቹ በአፓርታይድ ሥርዐት ወቅት ከነበረው ጋር ተስተካከለ። ከዚያም በኋላ ብልጫ አሳየ። የሚገርመው ኢ-እኩልነቱ በፍጥነት የጨመረው የደቡብ አፍሪካ አማካይ ዕድገት አመርቂ ነው በሚባልበት ወቅት ነበር። ድህነት ቀነሰ ቢባልም ፍጥነቱ እጅግ ዝግ ያለ ነበር። በርግጥ ጥቂት ጥቁር ልሂቃን እና ከመንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ነጋዴዎች በተለይ የጥቁሮችን የኢኮኖሚ ኃይል ለማሳደግ በወጣው Black Economic Empowerment ፖሊሲ ተጠቅመው የበለጸጉ ቢኾንም ለብዙኃኑ ደቡብ አፍሪካውያን አዲሱ የዴሞክራሲ ሥርዐት ያመጣው የኢኮኖሚ ጥቅም እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። በዚህም ምክንያት የብዙዎች ተስፋ ተቀጨ። ቁጣ እና ንዴት ጨመረ፤ ድህነት፣ ሥራ አጥነት እና የአገልግሎት አቅርቦት ችግር ተስፋፋ፣ በየታውንሺፑ በየጊዜው የሚደረጉ ከአገልግሎት አቅርቦት ችግር ጋራ የተገናኙ ዐመጾች ተበራከቱ። ለዚህ እና ለሌሎች ኢኮኖሚ ነክ ዐመጾች መንግሥት የሚሰጠው ምላሽ አንዳንዴ እንዳልተፈጠሩ እና እንዳልነበሩ አድርጎ መርሳት፣ አንዳንዴ ኃይል የተቀላቀለበት ጨካኝ ርምጃ መውሰድ፣ ምርጫ ሲደርስ ደግሞ ሥንዝር ጉቦ እየሰጡ ለማማለል መሞከር ነው። ለምሳሌ፦ እ.ኤ.አ ነሐሴ 2012 የደሞዝ ጭማሪ የጠየቁ በማሪካና አካባቢ በማዕድን ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ ጥቁር ሠራተኞች ላይ መንግሥት ተኩስ ከፍቶ 34 አድመኞችን ሲገድል 78 አቁስሏል።
ደቡብ አፍሪካ ዴሞክራሲ ስትጀምር ሌላው የተፈጠረ ነገር ወደ አገሪቱ የሚመጡ ስደተኞች ቁጥር (በተለይ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት) በፍጥነት መጨመር ነበር። የኤኤንሲ መሪዎች ቀስተ ደመናዋ አገር (the rainbow nation) የሚል አገሪቱ ብዙ ዘሮች፣ ብሔረሰቦች እና ጎሳዎች በሰላም፣ በፍትህ እና በፖለቲካ እኩልነት የሚኖሩባት መኾኗን የሚያበስር አካታች (inclusive) መመርያ ይዘው ሥልጣን ላይ ወጡ። በርግጥ ይህ አካታች እሴት የሚመለከተው ደቡብ አፍሪካውያንን ብቻ ይኹን ወይም የውጪ ዜጎችን ይጨምር ግልጽ አልነበረም። በደንብ አልተተነተነም፤ ክርክር አልተደረገበትም። ነገር ግን በተለይ በዴሞክራሲው የመጀመርያ ዓመታት የኮንግረሱ አመራሮች በተግባር ሐሳቡ የውጪ ዜጎችንም እንዲጨምር አድርገውት ነበር። በእነዚሁ ዓመታት ለበርካታ ስደተኞች የመኖርያ ፈቃድ ተሰጥቷል። ደቡብ አፍሪካ ነጻነቷን ስትቀዳጅ በብዙ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ ግጭት እሳቶች ይነዱ ነበር። ከእነዚህ ግጭቶች የሚያመልጡ በርካታ ስደተኞች አገሪቱን መጠለያ አደረጉ። በተጨማሪም ደቡብ አፍሪካ ከብዙ የአፍሪካ አገሮች የተሻለ የኢኮኖሚ የዕድገት ደረጃ ላይ ያለች እና የገቢ መሻሻል ዕድል የምትሰጥ በመኾኗ የኢኮኖሚ ስደተኞች ማግኔት ኾነች። ከሞዛምቢክ፣ ከዚምባቡዌ፣ እና ከኮንጎ በነፍስ ወከፍ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ አገሪቱ ገቡ። ከምዕራብ እና ምሥራቅ አፍሪካም ቢኾን ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ሰዎች ወደ ደቡብ አፍሪካ አቀኑ። ከእነዚህ ስደተኞች መካከል አብዛኞቹ ቀያቸው ያደረጓቸው ጥቁር ድኻ ደቡብ አፍሪካውያን የሚኖሩባቸውን ታውንሺፖች ነው። የስደተኞቹ የኢኮኖሚ ኹኔታዎች ከፍ እና ዝቅ ያለ ቢኾንም ጥናቶች እንደሚያሳዩት እነዚህ ስደተኞች በታውንሺፖች ያሉትን የኢኮኖሚ ችግሮች እና ኹከቶች ለመቋቋም ጠንካራ የዋስትና ማኅበራዊ መረቦችን ዘርግተዋል፤ በጥቃቅን ንግዶች እና በጥቁር ኢኮኖሚ በብዛት ይሳተፋሉ፣ እጅግ በዝባዥ በኾነ ዋጋ ተቀጥረው ሥራ ለመሥራትም አያቅማሙም።
በብዙ አገራት እንደምንመለከተው እነዚህ ሁለት ነገሮች- በመንግሥት የፖሊሲ ክሽፈት የተባባሰ ድህነት፣ ተስፋ መቁረጥ እና መጠነ ሰፊ ስደት- ሲገናኙ ማኅበራዊ ፈንጂ የመፈጠር ዕድሉ ከፍ ይላል። ፖለቲከኞች (ከፍተኛም ይኹን ዝቅተኛ እርከን ሥልጣን) በራሳቸው ድክመት የመጣ ችግርን ለመሸፈን ጣታቸውን ስደተኞች ላይ መጠቆማቸው ያልተለመደ ድርጊት አይደለም። በግጭት የሚጠቀሙ ነጋዴዎች (conflict entrepreneurs) ይህን አጋጣሚ አያልፉትም። ለምሳሌ፦ በ2008ቱ ኹከት ላይ የተሠሩ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከኤኤንሲ ቀበሌ አደራጆች እስከ የታውንሺፕ ፖለቲካ እና ማኅበራዊ መዋቅር አንቀሳቃሾች በኹከት ቅስቀሳ ላይ ተሰማርተው ነበር። እነዚሁ ጥናቶች እንደሚያሳዩት የደቡብ አፍሪካውያን የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ሲጨምሩ- የመዋቅሩ መሪዎች ድጋፍ እና ተደማጭነት እያሽቆለቆለ ሲመጣ - ስደተኞች ላይ የሚያደርጉት ቅስቀሳ ያይላል። የቅስቀሳዎቹ ዋነኛ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦ የደቡብ አፍሪካ ድኾች ከችግራቸው ሊወጡ ያልቻሉት ሥራቸውን በስደተኞች ስለሚነጠቁ ነው፤ ገቢያቸው ከስደተኞች በሚመጣ ፉክክር ይቀንሳል፤ በስደተኞች መብዛት ምክንያት በመኖርያ ቤቶች አቅርቦት ላይ የሚደርሰው ጫና ከፍተኛ ነው። እነዚህ በሙሉ የአስተዳደርን ክሽፈት የሚደብቁ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ የቀስተ ደመናዋ አገር የሚለው ሐሳብ ለደቡብ አፍሪካውያን እንጂ ለውጪ አገር ዜጎች አይሠራም የሚለው አጠቃላይ አመለካከት አግላይ ብሔረተኝነት (exclusive nationalism) በመፍጠር ልዩነቱን አባብሶታል። ከዴሞክራሲ የመጀመርያዎቹ ዓመታት ውጭ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት መሪዎች በንግግራቸው፣ በተግባራቸው እና በፖሊሲያቸው የቀስተ ደመናን ሐሳብ የውጪ ዜጎችን በሚያካትት ኹኔታ ለማስፋት ፍላጎት እንደሌላቸው አሳይተዋል።
የጥላቻ ቅስቀሳ፣ አሉታዊ እና አግላይ ብሔረተኝነት የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካለው ደኅንነትን የመጠበቅ ድክመት ጋር ተያይዞ በየጊዜው ስደተኛ ጠል ጥቃቶች እንዲጀመሩ እና በቀላሉ እንዲባባሱ ምክንያት ኾኗል። ለምሳሌ፦ የ2008ቱ ኹከት ሲቀጣጠል እና ሲስፋፋ የምቤኪ መንግሥት ለቀናት ከሩቅ ተመልካችነት ያለፈ ሚና አልነበረውም። በመጨረሻ ከብዙ ማመንታት በኋላ ኹከት ወዳለባቸው ሥፍራዎች ወታደሮችን በመላክ ጥቃቱን አስቁሞታል። የዙማ መንግሥትስ ይኼን ለማድረግ ምን ያህል ጊዜ ይፈጅበት ይኾን?

Tuesday, 7 April 2015

ኑክሌርን ለኢራን ያስተዋወቀችዉ ዩናይትድ ስቴትስ ናት :- አብይ1702 Via Deutsche Welle

የኢራንና የምዕራባዉያን ስምምነትና እድምታዉ

ኑክሌርን ለኢራን ያስተዋወቀችዉ ዩናይትድ ስቴትስ ናት።በ1950ዎቹ «አቶሚክ ለሠላም» በሚል መርሕ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢራን የሐይል ማመንጪያ ተቋም ማስገባት ጀምራ ነበር።የኑክሌር ተቋም ግንባታዉን ያቋረጠችዉ ደግሞ ማንም ሳይሆን እራስዋ ኢራን ነበረች

እነ ሳዑዲ አረቢያ የየመን ፖለቲከኞችን ጠብ አጡዘዉ ደሐይቱን ሐገር በቦምብ ሚሳዬል የማጋያታቸዉ ድፍረት፤የእኒያ ነባር ጠበኞች ነባር ጠብ የመናሩ ዉጤት መሆኑ አያጠያይቅም። ከፍልስጤም-እስራኤል እስከ ሊባኖስ፤ ከኢራቅ እስከ ሶሪያ፤ ከኮሪያ እስከ ዩክሬን፤ የዘለቀዉ የነባር ጠላቶች፤ ጠበኞችን የማጋጨት፤ ማጋደል፤ ማፋጀት ሴራ፤ ሽኩቻ፤ ሽሚያቸዉ በርግጥ ግሟል።የማጠፋፋታቸዉ ነባር ስልት ንረት የመን ላይ የሚያስከትለዉ ጥፋት መጠን ሲተነትን ግን ዋሽግተን-ብራስልሶች፤ ከቴሕራን፤ ሞስኮ ቤጂንጎች ጋር ጠብ ሽኩቻቸዉን ቢያንስ ላጭር ጊዜ እስወግደዉ ለጋራ ጥቅም እንደጨዋ ተደራድሩ። እንደ ብልሕ ተስማሙ ።
ኢራን፤ ዩናይትድ ስቴትስና ተከታዮችዋ
አያቶላሕ ሩሑላሕ ሆሚኒ የመሯቸዉ የኢራን እስላማዊ አብዮተኞች በ1979 (ዘመኑ በሙሉእንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) የንጉስ መሐመድ ሬዛ ሻሕ ፓሕላቪን አገዛዝ አስወግደዉ የቴሕራንን ቤተ-መንግሥት ከተቆጣጠሩ ወዲሕ ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ያልተወዛገቡ፤ያልተዛዛቱ፤ ያልተሻኮቱ፤ ያልተጋደሉ ያላጋደሉበት ዘመን የለም።
ከታጋች-አጋችቾ ድራማ እስከ ኢራን-ኢራቅ ጦርነት፤ ከፍልስጤም-እስራኤል ግጭት እስከ እስራኤል ሊባኖሶች ዉጊያ፤ ከአሜሪካ መራሹ የኢራቅ ወረራ እስከ -ሶሪያ ጦርነት፤ አሁን ደግሞ በየመኑ ጦርነት አልፎ አልፎ በቀጥታ፤ ሁል ጊዜ በተዘዋዋሪ የየሐገሩን ወይም የየአካባቢዉን ተቀናቃኝ ሐይላትን መደገፍ፤ ጠበኞችን ማጋጨት፤ የተጋጩትን ማጋደል የቴሕራን ዋሽግተኖች ጥቅም ማስከበሪያ ሥልት ነዉ።ሰላሳ ስድስት ዘመን።
የኢራን የኑክሌር መርሐ ግብር የሁለቱ ሐገራትና የየወዳጆቻቸዉ ፖለቲከኞች የርዕዮተ-ዓለማዊ፤ ፖለቲካዊና ስልታዊ ጠላትነታቸዉ አንዱ ምክንያት እንጂ በርግጥ የጠላትነታቸዉ መሠረት አይደለም።መሠረታዊዉን «ጠላትነት» ለማባስ፤ ምናልባትም በቀድሞዉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት በጆርጅ ደብሊዉ ቡሽ ዘመን እንደተሞከረዉ ቀጥታ ጦርነት ለመለኮስ ግን በቂ ሰበብ ነበር።ነዉም።
ሩሲያ፤ ዩናይትድስ ስቴትስና ምዕራብ አዉሮጳ
ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ፍፃሜ ወዲሕ የወዳጅነት መንፈስ ተላብሶ የነበረዉ የሩሲያ፤የዩናይትድ ስቴትስና የምዕራብ አዉሮጶች ግንኙነት በሶሪያዉ ጦርነት ሰበብ መደፍረስ ጀምሮ፤ በዩክሬን ፖለቲካዊ ቀዉስ ምክንያት ወደ ቅጣት-ዉግዘት፤ ወደ ዛቻ ፉከራ ንሮ የቀዝቃዛዉ ጦርነት ዘመንን መልክና ባሕሪ ይዟል።
ቻይና፤ ዩናይትድ ስቴትስና ምዕራብ አዉሮጳ
ማኦ ዜዱንግ የመሯቸዉ የቻይና ኮሚንስቶች ሕዝባዊት ሪፕብሊክ ቻይናን ከመሠረቱ ከ1949 ወዲሕ የኮሚንስት ካፒታሊስቱን ጠብ የተቀየጠችዉ ቻይና ከዩናይትድ ስቴትስና ዩናይትድ ስቴትስ ከምትመራቸዉ መንግሥታት ጋር ሠላም ሆና አታዉቅም።
የቤጂንግ-ዋሽግተን-ብራስልስ ፖለቲከኞች ከኩሜንታግ-ኮሚንስቶች ዉጊያ፤ እስከ ታይዋን-ቻይናዎች ግጭት፤ ከኮሪያ ልሳነ-ምድር ጦርነት እስከ ቬትናም መወረር፤ ከሲኖ-ጃፓን እስከ ሲኖ-ሕንድ ዉዝግብ የዘለቀዉ ጠብ ዛሬም በኮሪያ ልሳነ ምድር ዉጥረት ሰበብ ሞቆ እየቀዘቀዘ ለሑዋይ-አፐል የንግድ ሽኩቻ ተርፏል።
ኢራን፤ ምሥራቅና ምዕራቦች
የኢራን እና ዩናይትድ ስቴትስ የምትመራቸዉ ምዕራባዉያን መንግሥታት፤ የኢራቅና የሶሪያ እስላማዊ መንግሥት ISIS የተሰኘዉን አሸባሪ ቡድንን በጋራ ለመዉጋት ያልተፈራረሙት ስምምነት፤ ያላወጁት ግንባር ፈጥረዋል።ወይም ለመፍጠር ተገደዋል።ለነባር መርሕ፤ አቋም ተገዢዎች ግር የሚያሰኘዉ «ትብብር» ግን ለጊዚያዊ ጥቅም ከመቻቻል ባለፍ የአያቶላሕ ሆሚንዋን ትልቅ ሰይጣን ከፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽዋ የሰይጣን መዘዉር (ዛቢያ)ጋር የሚያስታርቅ አይደለም።
ከ1979 ጀምሮ ዋሽግተን፤ ለንደን ብራስልሶች ፊታቸዉን ያዙሩባት ኢራን ሠልፏን ከምሥራቆቹ ጋር አለማስተካከል አትችልም ነበር።የዲፕሎማሲ፤የጠመንጃ ቤንዚን ሽያጩ ወዳጅነት በሶሪያና በዩክሬን ጦርነቶች ሰበብ የምስራቅ-ምዕራቦቹ ልዩነት ሲሰፋ ይበልጥ ተጠናክሯል።
ድርድርና ዉጤቱ
በየዘመኑ፤በየአካባቢዉ፤ በየምክንያቱ የሚወዛገቡ፤ የሚሻኮቱ፤ የሚዛዛቱ፤ እንዳዴም የሚጋጩት ተቀናቃኝ መንግሥታት በጠብ ቁርቁሳቸዉ መሐል እንደ ፖለቲካዉ ወግ ድርድርን አላቆሙም።በተለይ የኢራን የኑኬሌር መርሐ-ግብር የየዉዝግብ ጠቡ አቀጣጣይ ከምሱር ከሆነ ወዲሕ እየተቀጣጡ፤እየተዛዛቱእየተጋደሉ፤ እያጋደሉም ደርድሩን አላቋረጡም።እስራ-ሁለት ዓመት።
ባለፈዉ ሳምንት ሐሙስ ተስማሙ።ሉዛን ሲዊዘርላንድ።«ዛሬ ወሳኝ እርምጃ ወስደናል።ለአጠቃላዩ የጋራ የድርጊት መርሐ-ግብር በሚረዱ ቁልፍ ጉዳዮች መፍትሔዎች ላይ ተስማምተናል።ከዚሕ ያደረሰን የሁሉም ወገኖች ፖለቲካዊ ፅናት፤መልካም ፈቃድና ብርቱ ሥራ ነዉ።በዚሕም ምክንያት ሁሉም መልዕክተኞች ላሳዩት ያላሰለሰ ፅናት እናመስግናቸዉ።ይሕ (ስምምነት) ከዚሕ ቀደም ለተደረገዉ የመጨረሻ አጠቃላይ የድርጊት መርሐ ግብር መሠረት የሚጥል ነዉ።»
የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ግንኙነት ሐላፊ ወይዘሮ ፌደሪካ ሞሕግሪኒ።ኢራኖች በአደባባይ ፈነደቁ።ማዕቀብ ሊነሳ ነዉ።መሪዎቻቸዉን አወደሱ።እንዲሕ እንደ ድሕረ-1979ኙ የኢራን አብዮት የመሪና የርዕዮተ-ዓለም ለዉጥ ከማምጣቱ፤ በዉጤም የቴሕራን ዋሽግተኖች ወዳጅነት በጠላትነት ከመለወጡ በፊት ኑክሌርን ለኢራን ያስተዋወቀችዉ ዩናይትድ ስቴትስ ናት።በ1950ዎቹ «አቶሚክ ለሠላም» በሚል መርሕ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢራን የሐይል ማመንጪያ ተቋም ማስገባት ጀምራ ነበር።
የኑክሌር ተቋም ግንባታዉን ያቋረጠችዉ ደግሞ ማንም ሳይሆን እራስዋ ኢራን ነበረች።የመጀመሪያዉ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪ አያቶላሕ ሩሑላሕ ኾሚኒ የኑኬሌር ተቋሙ ጦር መሳሪያ ሊመረትበት እንደሚችል ሲያዉቁ «እንዲሕ አይነት መሳሪያ በእስልምና ሐራም ነዉ» ብለዉ አስቆሙት።ከሆሚኒ ሞት በሕዋላ ግን የኾሚኒ ተከታዮች እስራኤልን ጨምሮ ብዙ ሐገራት ያን አጥፊ ቦምብ መታጠቃቸዉን ሲሰሙ የመሪያቸዉን ዉግዘት አፍርሰዉ ለሠላም ያሉትን የኑክሌር መርሐ ግብር ቀጠሉ።
ከምዕራባዉያን ጋር ወትሮም ያልቀዘቀዘዉ ጠብ-ሽኩቻም ባሰ።ባለፈዉ ሳምንት ግን ጠቡ ባይጠፋ በረደ።በቀደም ቴሕራን ሲገቡ-ከአዉሮፕላን ማረፊያ እስከ መሐል ከተማ ሕዝባቸዉ በሆታ-እልልታ-የተቀበላቸዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር መሐመድ ጀዋድ ሳሪፍከሉዛን ከመነሳታቸዉ በፊት «ማንም የማይፈልገዉን አንፈልግም» አሉ።ከሁሉም በላይ ከተፈለገ ክብርን በጠበቀ ድርድር የማይፈታ ችግር የለም።
«እርምጃዎቻችንን ገቢር ሥናደርግ በእስላማዊት ሪፐብሊክ ኢራን ላይ ምንም አይነት ማዕቀብ አይኖርም።ይሕ በኔ እምነት ታላ ቅ እመርታ ነዉ።ለማንም የማይጠቅመዉን፤ለአዉደማዊ ጦር መሳሪያ አጋጁ ስምምነት የማይጠቅመዉን፤ጉዳዩ ለሚመለከታቸዉ ወገኞች፤ ለማንም የማይጠቅመዉን ዑደት አቁመናል።በዚሕ ሒደት መጨረሻ በድርድርና ክብርን በጠበቀ ግንኙነት ችግሮችን ማስወገድ ፤ አድማስን መክፈት፤ እና ወደፊት መራመድ እንደምንችል እናሳያለን።»
ከዩናይትድ ስቴትስ ፖለቲከኞች ቀኝ አክራሪዎቹ የቲፓርቲና የሪፕብሊካን ፓርቲ አባላት በሰምምነቱ አለመደሰታቸዉ አይቀርም።የዋሽግተን መሪዎች ደስታ ግን ከቴሕራን ፖለቲከኞች ያነሰ አይደለም።ፕሬዝዳንት ባራክ ኦቦማ።«ዛሬ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ከወዳጆችዋና ተባባሪዎችዋ ጋር ሆና ከኢራን ጋር ታሪካዊ መግባባት ላይ ደርሳለች።ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ገቢራዊ ከሆነ ኢራን የኑክሌር ጦር መሳሪያ እንዳታገኝ ያግዳታል።እንደ ፕሬዝዳንትና የጦር ሐይሎች ጠቅላይ አዛዥነቴ የአሜሪካንን ሕዝብ ፀጥታና ደሕንነት ከማስጠበቅ የበለጠ ሐላፊነት የለብኝም።ይሕ የመግባቢያ ስምምነት ከመጨረሻዉ አጠቃላይ ስምምነት ላይ ከደረሰ ሐገራችንን፤ ወዳጆቻችንን እና ዓለማችንን ይበልጥ አስተማኝ ያደርጋቸዋል።»
ከሶማሊያ እስከ የመን፤ ከደቡብ ሱዳን እስከ ኬንያ፤ከኮንጎ እስከናይጄሪያ፤ ከማሊ እስከትሪፖሊ፤ ከጋዛ እስከ ሲና፤ ከሶሪያ እስከ ኢራቅ፤ ከአፍቃኒስታን እስከ ከዩክሬን ከጦርነት፤ ሽብር ፀረ ሽብር ግድያ ሌላ በጎ ነገር ለማይሰማዉ ዓለም ሥምምነቱ የሩቅ እና ትንሽም ቢሆን በርግጥ ተስፋ ነዉ።
ተስፋ እዉን መሆን አለመሆኑ የሚታወቀዉ ደግሞ የኢራንም፤የዋሽግተንም ፖለቲከኞች በየፊናቸዉ እንዳሉት ገቢራዊ ሲሆን ነዉ።በሎዛኑ ድርድር-ስምምነት የተካፈሉት የፈረንሳዩ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሎራ ፋቢዮስ እንዳሉት ግን ተደረራዳዊዎች ከዚሕ ስምምነት መድረሳቸዉ ራሱ ታላቅ እርምጃ ነዉ።«ይሕ ስምምነት ያለምንም ጥርጥር መልካም ጉዳዮችን ያካተተ የመሠረት ድንጋይ ነዉ።ይሁንና አሁንም ብዙ ሥራ ይቀረናል።ምክንያቱም እስከ ሰኔ ሠላሳ ብዙ ነገሮችን ማጠናቀቅ አለብንና።»
የጀርመኑ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ቫልተር ሽታይን ማየር በፋንታቸዉ ድፍን አስራ-ሁለት ዓመት አላላዉስ ያለዉ እንቅፋት ተወገደ ነዉ-ያሉት።የስምምነቱ አስደሳችነት አያጠራጥርም።
«(ስምምነቱ) አንድ ታላቅ ርምጃ ወደፊት መሆኑ ምንም ጥርጥር የለዉም።አሁን የተወገዱት እንቅፋቶች እስካሁን ሁነኛ ስምምነት እንዳይደረግ ቢያንስ ላለፉት አስራ ሁለት ዓመታት ሁሌም አደናቃፊ የነበሩ ናቸዉ።እንደሚመስለኝ እስካሁን ያለዉ ዉጤት አስደሳች ነዉ።»
ከዩናይትድ ስቴትስ፤ከፈረንሳይ እና ከጀርመን ጋር አምስት ሲደመር አንድ የተሰኘዉ ቡድን የሚያስተናብራቸዉ የብሪታንያ፤ የሩሲያና የቻይና ፖለቲከኞችም በስምምነቱ መደሰታቸዉን አልሸሸጉም።የአንዲት ሐገር አንድ መንግሥት ፖለቲከኞች ግን በስምነቱ ተከፍተዋል።የዩናይትድ ስቴትስና የምዕራብ አዉሮጳ ሐገራት የቅርብ ወዳጅ የእስራኤል ፖለቲከኞች።ቃል አቀባይ ማርክ ሬጌቭ እንዳሉትማ ስምምነቱ ወደ አደገኛ አቅጣጫ የሚያጉዝ ነዉ።
«ይሕ የመግባቢያ ዉል ወደ በጣም፤በጣም አደገኛ አቅጣጫ የሚያመራ እርምጃ ነዉ።ኢራን በጣም ዉድ ከሆነ የኑክሌር መዋቅሯ ጋር እንድትቀጥል የሚያደርግ ነዉ።ከኢራን የኑክሌር አንዱንም እንኳ አያዘጋም።ኢራን ዩራኒየም ማብላላቷን፤ በሺሕ የሚቆጠሩ ማብላያዎችዋን እንደያዘች እንድትቀጥል የሚያደርግ ነዉ።ከዚሕ በተጨማሪ ኢራን የተሻለ ማብላያ እንዲኖራት የምታደርገዉን ምርምር እንድትቀጥል የሚፈቅድ ነዉ።»
በ1972 የያኔዉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሪቻርድ ኒክሰን ሞስኮ ድረስ ተጉዘዉ ከያኔዉ የሶቬት ሕብረት መሪ ሊዮኒድ ቭሬዥኔቭ ጋር የመጀመሪያዉን የሥልታዊ ጦር መሳሪያ እነሳ ስምምነት ተፈራርመዋል።ሶልት አንድ።በ1987 የያኔዉ የሶቭየት ሕብረት መሪ ሚኻኤል ጎርቫቾቭ ዋሽግተን ድረስ ተጉዘዉ ከያኔዉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬጋን ጋር የኑክሌር ጦር መሳሪያ ዉል ተፈራርመዋል።ዉል ስምምነቱ ለዓለም ሠላም አደገኛ ከነበረ ካሁኑ ስምምነት ይልቅ የያኔዉ ሲበዛ አደገኛ በሆነ ነበር።አልሆነም።ካንዲት ደካማ ሐገር ጋር የተደረገዉ ያሁኑ ስምምነት ፕሬዝዳንት ኦባማ እንዳሉት ከእስካሁኑ አስጊ የሚሆንበት ሰበብ ምክንያት በርግጥ ግራ ነዉ።

Saturday, 4 April 2015

Wanted for Kenya attack in Garissa: Who is Mohamed Kuno?

Wanted for Kenya attack in Garissa: Who is Mohamed Kuno?

  • 2 April 2015
  •  
  • From the sectionAfrica
Kenya university attack: Wanted poster showing Mohamed Mohamud, alias Dulyadin alias Gamadhere - ALLEGED to be the mastermind behind the attack on the campus by Islamist militants
The Kenyan government has named Mohamed Kuno as the mastermind behind the Garissa University College attack and has put a $215,000 (£145,000) reward for his capture.
He has several aliases but is best known as Mohamed Dulyadin, which means ambidextrous in the Somali language. His exact age is not known but is thought to be in mid-30s.
Kuno is a Kenyan-Somali and was a headmaster at a madrassa, or Islamic school, in Garissa, Kenya until 2007.
But then he crossed the border into Somalia to join the Union of Islamic Courts (UIC), which at one point controlled much of the country.

Joined al-Shabab

When the UIC collapsed he joined the militant group Hizbul Islam, which in 2010 merged with al-Shabab.
A BBC Somali service reporter says that Kuno is well-known as a hardliner in Somalia and is one of al-Shabab's leading operatives in the southern Jubaland region, which shares a long border with Kenya.
He is alleged to have been behind several attacks on Kenyan soldiers who are fighting al-Shabab in Jubaland. He is also blamed for attacks on Kenyan civilians in Kenya itself.